Tuesday, 05 May 2020 20:24

ቧንቧ ነኝ

Written by

አቤት በአንቺ ላይ ያለው የቃሉ መገለጥ! 
አቤት የተሰጠው ህይወትሽ! 
አቤት በእግዜር ህዝብ መሃል ይዘሽው ምትገቢው ድባብ!
አቤት ቃላቶችሽ! 
አቤት ምክር አሰጣጥሽ! 
አቤት አስተምህሮሽ! 
አቤት! አቤት! አቤት!
 
ተው! ተው አትካቡኝ፣
 ትዕቢት እንዳይንደኝ
ተው! ተው አታግዝፉኝ፣ 
እኔነት እንዳያንቀኝ
 
እኔ እኮ ቧንቧ ነኝ፣ 
በበላይ ትዕዛዝ የተተከልኩኝ 
እኔ እኮ ባሪያ ነኝ፣ 
ተጠሪ አዛዥ ያለኝ
እኔ እኮ አውራጅ ነኝ፣ 
ያለ ውሃው ምንጭ ዋጋ የሌለኝ
 
ተው! አትካቡኝ፣ 
ትምክህት እንዳይነቅለኝ
 
ብናገር፣ ሞገሴ
ባስተምር፣ ጥበቤ
ቢወራልኝ፣ ክብሬ
ብመክር፣ ተመክሬ
ብምር፣ ተምሬ
ብወድድ፣ ተፈቅሬ
ብታይ፣ መድመቂያዬ
ብመካ፣ በጌታዬ
ቧንቧ ብሆን፣ በርሱ ተተክዬ
ባፈስ፣ ከምንጩ መንጭቼ
 
አንድን ነገር ልብ አልኩ በዘመኔ የውሃን ቧንቧ ሲያመሰግን ያየሁት የለም እኔ
 
ዋናው ውሃው ነው! 
ዋናው ከእርሱ ነው!
ዋናው በእርሱ ነው! 
ዋናው ለእርሱ ነው!
 
ዋናዬ 'ዋና' ነው!
 
ይልቅስ......
 
ባልተጨበጠ ደስታ እንዳልታበይ፣ 
አውቃለሁ ብዬም ማወቅ እንዳላቆም፣ 
ከእርሱ ዝቅ ብዬ እንድማር እንደ ማሪያም፣ 
እንዳልቅበዘበዝ እንደ ማርታ፣ እንድጀግን እንደ ጢሞቲዮስ፣ 
ትሁት እንድሆን እንደ ክርስቶስ፣ 
እንዳውቅ እንደ ጳውሎስ፣ 
ልቤን እንዲከፍተው እንደ ሊዲያ፣ 
ያለ ግዜዬ እንዳልታይ እንዳልታበይ  
ፀልዩኝ ማልዱልኝ! 
 
 
መታሰቢያነቱና የፀሎት ሸክሙ ለሁላችን፣ በተለይም ለሚያገለግሉን የእግዜር ባሪያዎች ይሁንልኝ። 
 
ቤ.ካ
2012 ተፃፈ

white-200.png

Serving Ethiopian women by encouraging and exemplifying vulnerable, thought-provoking conversations around the Gospel of Jesus Christ, the mission of the
Church, and the life of a Christian.

Address
:
Golagul Tower
Addis Ababa, Ethiopia

Emailinfo@selahethiopia.org
selahforethiopia@gmail.com

Follow Us

Subscribe to emails from Selah

We have officially launched our website and all our social media platforms. Please join us, follow, and share. Subscribe to our newsletter bringing you regular updates, resources, and everything in between!

Copyright © 2023 Selah Ministries.
Address: Addis Ababa, Ethiopia 
Emailinfo@selahethiopia.org